Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/orthodox1/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tg-me/post.php on line 50
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 | Telegram Webview: orthodox1/13088 -
Telegram Group & Telegram Channel
ቤተልሔም ፣ ዮርዳኖስና ቀራንዮ
በልደት ፣ በጥምቀትና በስቅለት
የአምላክ «መራቆት»
━━━✦༒༒✦━━━

መኑ ይሁበኒ ሥጋሁ ለኢየሱስ
ከመ እክድን ዕርቃኖ በልብስ
ለዘከደነ ዕርቃንየ በዮርዳኖስ

[ በዮርዳኖስ እርቃኔን የሸፈነውን እርቃኑን በልብስ እሸፍን ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ ማን በስጠኝ ?]

የዘፍጥረት መጽሐፍ ቀዳሚ መልእክት እንዲህ የሚል ነው «ወምድርሰ ሀለወት እምትካት ዕራቃ ☞ ምድር ግን ከቀድሞው ራቁትዋን ነበረች» ይህም ከአዝርዕት ከአትክል ከሰው የተራቆተች ሆና ባዶ ፣ ከንቱ ሆና ምድረ በዳ ነበረች ማለቱ ነው [ዘፍ ፩፥፪]

የፍጥረቱ አክሊልና የምድራችን ጌጥ ሆነን የተፈጠርነው እኛ የሰው ልጆችም ራቁትነታችን በብርሃን መጋረጃ የተሸፈነ ነበር ፤ ኋላ በበደላችን ምክንያት ከጸጋ ልጅነት ከአምላክ ባለሟልነት ስንርቅ ተራቁተን ቀረን እንጂ "አእመሩ ከመ ዕራቃኒሆሙ እሙንቱ ☞ ዕራቁታቸውን እንደሆኑ አወቁ" እንዲል [ዘፍ ፫፥፮]

እግዚአብሔርን ለመምሰል ብርሃን ተጎናጽፎ ይኖር የነበረው ሰብእናችን በበደሉ ምክንያት ዕርቃናቸውን የሚኖሩ እንሰሳትን መሰለ።

አባ ጊዮርጊስ ይህን ርደት እንዲህ ገልጦታል ፦ “ምንት ውእቱ ተመስሎ እንስሳ ዘእንበለ ተከሥቶ ዕርቃኑ ማእከለ ዕፀዊሃ ለገነት ሶበ ነፍጸ አጽፈ ብርሃን ዘላዕሌሁ ኀደጎ አጽፈ ብርሃን ⇨ በገነት ዛፎች መካከል ዕርቃኑን ሆኖ ከመተየት በስተቀር እንስሳን መምሰል ምንድ ነው? የብርሃን ልብስ ከበላዩ ላይ በተገፈፈ ጊዜ የብርሃን መጐናጸፊየው ተለየው” (መጽሐፈ ምሥጢር)

በፍና ሠርክ በድምጸ ሰኮና ብእሲ ‘እንደምን ባለ አነዋዋር አላችሁ ይሆን ? በክብር ወይስ በኃሣር ? ’ እያለ ፈልጎ አገኘንና ስለመተላለፋችን ፈርዶ ከቀደመ ክብራችን አውርዶ ከገነት አስወጣን፤ ያን ጊዜ በጊዜአዊነትም ቢሆን ሐፍረት መክደኛ ዕርቃን መሸፈኛ አበጀልን! "ወገብረ እግዚአብሔር ለአዳም ወለብእሲቱ አእዳለ ዘማእስ ወአልበሶሙ … እግዚአብሔር አምላክም ለአዳምና ለሚስቱ የቁርበትን ልብስ አደረገላቸው፥ አለበሳቸውም።” [ዘፍ ፫፥፳፩]

ኋላ በምስጋና መብረቅ የተጋረደና በእሳት ደመና የተሸፈነ አምላክ ወልደ አምላክ የተስፋውን ቃል ለመፈጸም ከውድቀታችን ሊያነሳን ያን የተራቆተ ሥጋችንን ለበሰልን። የሚካኤል ሠራዊት በፍርኃት የገብርኤል ሠራዊት በመንቀጥቀጥ የሚያመሰግኑት እርሱ ዕርቃኑን በመካከላችን ተገኘ።

🍁 ወበቤተልሔም ወጽአ እምከርሰ እሙ ዕራቁ (በቤተልሔም ከእናቱ ማሕፀን ዕርቃኑን ተወለደ)

መጽሐፍ "ዕራቅየ ወፃእኩ እምከርሠ እምየ" እንዳለ እኛን በሚመስልበት የተዋህዶ ግብር ከድንግል እናቱ ማሕፀን ዕርቃኑን ተወለደ፤ ከመለኮቱ ሳይራቆት (ዕሩቅ ብእሲ ሳይሰኝ) ከሥጋ ልብስ ባዶ ሆኖ ተራቁቶ ፣ ክብሩን በፈቃዱ ትቶ በትህትና ወደምድራችን መጣ። ይህን ሥጋችንን ለብሶ የሰው ልጅ መባሉ ያንን የሰማይ ክብር እርሱን በጸጋ ለብሰን ትርሲተ ወልድ / የሥጦታ ልጆቹ ሊያሰኘን ነውና።

የመጽሐፉም ምስክርነት እንዲህ የሚል ነው "አሰረቶ መንኮብያቲሁ ወአስከበቶ ውስተ ጎል ወጠብለለቶ በጽርቅት ⇨ አውራ ጣቱን አሰረችው ፣ በግርግም አስተኛችው፣ በመጠቅለያም ጠቀለለችው” [ሉቃ ፪፥፯]

የ፲፭ ዓመቷ ገሊላዊት ብላቴና እናቱ ድንግል ማርያም በከብቶቹ ማደርያ ስትወልደው ለብኩርናው አውራ ጣቱን አሥራ፣ የተራቆተ ሰውነቱን በጨርቅ ጠቅላላ ፣ ለመኝታው ግርግም አሰናድታ ባላትና ባገኘችው ተቀበለችው። ይህም ለእኛ የተከፈለው ካሣ እረኞችም ምልክት እንዲሆናቸው በመልአኩ በኩል ‘እሱረ መንኮብያት ፣ ስኩብ ውስተ ጎል ፣ ጥብሉል በአጽርቅት (አውራ ጣቱ የታሠረ ፣ ከግርግም የተኛ ፣ በጨርቅ የተጠቀለለ) ሕፃን በበረቱ ታገኛላችሁ’ ተባሉ። [ሉቃ ፪፥፲፪]

ልጇን ጌታዬ የምትል ብቸኛዋ የፈጣሪ እናቱ የአምላክ ወላዲቱ ለዕርቃኑ መክደኛ የበለስ ቅጠል ስላገኘችበት ተኣምራታዊ መንገድ በቤተክርስቲያናችን ቅዱስ ትውፊት
እንዲህ የሚል አብነት አለ
«በለሶን ዕፀ አእምሮ የሚባለው ነው፤ ይህ የገነት በለስ አዳምና ሔዋን ፍሬውን በልተው ቅጠሉን የለበሱት ኋላም የልደት ዕለት በተኣምራት መልአክ (ቅዱስ ገብርኤል) አምጥቶላት ዳግሚት ሔዋን ድንግል ማርያም ለልጇ ለዳግማይ አዳም ሥግው ቃል ክርስቶስ ያለበሰችው ነው፤ ቅዱስ ያሬድ በድጓው "ከደነቶ እሙ ቄጽለ በሰሶን" እንዳለው። ስለዚህ ምሥጢር ብዙዎች ብዙ ብለዋል!

ባለቅኔው ፦
በለሰ ገነት ለአዳም ወሔዋን መቲሮቶሙ
መንክረ ልደት አምላከ መንገሌሆሙ ሰሐበ
ወገብርኤልሃ ዜናዊ ቀጸበ
እንተ ከመዝሰ ግብር እምከመ ለአዳም ተውህበ
ወረከበት ሔዋን ዘኢተረክበ
ካዕበ ይስሐብ ኀቤሆሙ አበ
ለበለሰ ይምትርዎ ካዕበ

ደራሲው ፦
ሰላም ለኵልያቲክሙ ዕሩያነ አካል ወአምሳል፥
አቅርንተ ነቢያት ሥላሴ ዘድምጽክሙ ወንጌል፥
ኢሳይያስ ጸርሐ ወይቤ ውስተ መካነ ላሕም ጎል፥
ገብርኤል አወፈየኒ ሕፃነ ማርያም ድንግል፥
በቆጽለ በለሶን ክዱን ወበጸርቅ ጥብሉል

🍁 ወበዮርዳኖስ ተጠምቀ በማይ ዕራቁ (በዮርዳኖስ ዕርቃኑን በውኃ ተጠመቀ)

ለኃጢዓታችን ሥርየት የሚሆን በግዕ ዘመስዋዕት፣ ለነፍሳችን ጠባቂዋ እረኛ ሊቀ ኖሎት፤ ወልዱ ለቡሩክ: ከሣቴ ብርሃን የዓለም መድኃኒት በባርያው በዮሐንስ እጅ እንዲጠመቅ ወደ ዮርዳኖስ ሲገባ ከልብሱ መራቆቱን የአበው መጽሐፍ እንዲህ ይገልጣል

"አስተርአየ በውስተ ዮርዳኖስ እንዘ ክሡት ዕርቃኑ ለተጠምቆ ⇨ ለመጠመቅ ራቁቱን በዮርዳኖስ ባሕር ውስጥ ታየ" (መጽሐፈ ምሥጢር)

የዮርዳኖስ ጥምቀት የሁላችን ዕርቃን የተከደነበት ነው።

🍁 ወበቀራንዮ ሰቀልዎ ዲበ ዕፅ ዕራቆ (በቀራንዮ በእንጨት ላይ ዕርቃኑን ሰቀሉት)

አባ ጊዮርጊስ ስለዚህም እንዲህ ብሏል “ወበከመ ተከሥተ ዕርቃነ አዳም ማእከለ ዕፀዊሃ ለገነት ከማሁ ተከሥተ ዕርቃነ ትስብእቱ ለመድኃኒነ ማዕከለ ጉባኤሆሙ ለማኅበረ እስራኤል ⇨ አዳም በገነት ዛፎች መካከል ርቃኑን እንደታየ እንደሁም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ በሰውነቱ በአይሁድ ጉባኤ መካከል ዕርቃኑን ሆኖ ታየ” (መጽሐፈ ምሥጢር)
በደራስያኑም የመልክእ ምስጋና እንዲህ ተገልጧል፦

ሰላም ለዕርቃንክ እምልብሰ እልታሕ ወሰንዱን
እስከነ ሰሐቁ ላዕሌከ ሐራ ጲላጦስ መስፍን
ክርስቶስ ክቡር በቅድመ አይሁድ ምኑን
ክድነኒ እግዚኦ ልብሰ ተፋቅሮ ብርሃን
እስመ ፍቅር ተዓቢ እምኵሉ ሥልጣን
[መልክኣ ማኅየዊ ዘውእቱ መልክአ ኢየሱስ ካልእ]

ሰላም ለዕርቃንከ ዘአዕረቅዎ አይሁድ፤
እምልብሰ ምድራዊ ግዙፋነ ክሣድ፤
ዕሥራኤል እሙንቱ ሕዝብ ክቡድ፤
ተማኅፀነ በዕርቃንከ ከመ ትዕቀበነ ወልድ፤
አንተ አቡነ ወንሕነ ውሉድ። [መልክኣ ቅንዋት]

ቅዱስ ያሬድም በፋሲካው ድጓ እንዲህ ይላል
“ሰአሎ ዮሴፍ ለጲላጦስ ወይቤሎ
#ሀበኒ_በድኖ_ለኢየሱስ
#ከመ_እክድን_ዕቃርኖ_በልብስ
#ለዘከደነ_ዕርቃንየ_በዮርዳኖስ - ዮሴፍ ለጲላጦስ እንዲህ አለው፡- በዮርዳኖስ እርቃኔን የሸፈነውን እርቃኑን በልብስ እሸፍን ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ ስጠኝ”

ዮሴፍና ኒቆዲሞስ እንደ ሰብአ ሰገል ምንኛ እድለኞች ናቸው? የአምላኩን እርቃን የሚሸፍን የራሱን ዕርቃን የሚከድን ነው።

እነርሱስ ከመስቀል ለማውረድ በአዲስ መቃብር ለማኖር ዕርቃኑን ለመክደን ሰውነቱን ለመሸፈን ጠይቀው ተፈቀደላቸው!

ታዲያ እኛስ …



tg-me.com/orthodox1/13088
Create:
Last Update:

ቤተልሔም ፣ ዮርዳኖስና ቀራንዮ
በልደት ፣ በጥምቀትና በስቅለት
የአምላክ «መራቆት»
━━━✦༒༒✦━━━

መኑ ይሁበኒ ሥጋሁ ለኢየሱስ
ከመ እክድን ዕርቃኖ በልብስ
ለዘከደነ ዕርቃንየ በዮርዳኖስ

[ በዮርዳኖስ እርቃኔን የሸፈነውን እርቃኑን በልብስ እሸፍን ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ ማን በስጠኝ ?]

የዘፍጥረት መጽሐፍ ቀዳሚ መልእክት እንዲህ የሚል ነው «ወምድርሰ ሀለወት እምትካት ዕራቃ ☞ ምድር ግን ከቀድሞው ራቁትዋን ነበረች» ይህም ከአዝርዕት ከአትክል ከሰው የተራቆተች ሆና ባዶ ፣ ከንቱ ሆና ምድረ በዳ ነበረች ማለቱ ነው [ዘፍ ፩፥፪]

የፍጥረቱ አክሊልና የምድራችን ጌጥ ሆነን የተፈጠርነው እኛ የሰው ልጆችም ራቁትነታችን በብርሃን መጋረጃ የተሸፈነ ነበር ፤ ኋላ በበደላችን ምክንያት ከጸጋ ልጅነት ከአምላክ ባለሟልነት ስንርቅ ተራቁተን ቀረን እንጂ "አእመሩ ከመ ዕራቃኒሆሙ እሙንቱ ☞ ዕራቁታቸውን እንደሆኑ አወቁ" እንዲል [ዘፍ ፫፥፮]

እግዚአብሔርን ለመምሰል ብርሃን ተጎናጽፎ ይኖር የነበረው ሰብእናችን በበደሉ ምክንያት ዕርቃናቸውን የሚኖሩ እንሰሳትን መሰለ።

አባ ጊዮርጊስ ይህን ርደት እንዲህ ገልጦታል ፦ “ምንት ውእቱ ተመስሎ እንስሳ ዘእንበለ ተከሥቶ ዕርቃኑ ማእከለ ዕፀዊሃ ለገነት ሶበ ነፍጸ አጽፈ ብርሃን ዘላዕሌሁ ኀደጎ አጽፈ ብርሃን ⇨ በገነት ዛፎች መካከል ዕርቃኑን ሆኖ ከመተየት በስተቀር እንስሳን መምሰል ምንድ ነው? የብርሃን ልብስ ከበላዩ ላይ በተገፈፈ ጊዜ የብርሃን መጐናጸፊየው ተለየው” (መጽሐፈ ምሥጢር)

በፍና ሠርክ በድምጸ ሰኮና ብእሲ ‘እንደምን ባለ አነዋዋር አላችሁ ይሆን ? በክብር ወይስ በኃሣር ? ’ እያለ ፈልጎ አገኘንና ስለመተላለፋችን ፈርዶ ከቀደመ ክብራችን አውርዶ ከገነት አስወጣን፤ ያን ጊዜ በጊዜአዊነትም ቢሆን ሐፍረት መክደኛ ዕርቃን መሸፈኛ አበጀልን! "ወገብረ እግዚአብሔር ለአዳም ወለብእሲቱ አእዳለ ዘማእስ ወአልበሶሙ … እግዚአብሔር አምላክም ለአዳምና ለሚስቱ የቁርበትን ልብስ አደረገላቸው፥ አለበሳቸውም።” [ዘፍ ፫፥፳፩]

ኋላ በምስጋና መብረቅ የተጋረደና በእሳት ደመና የተሸፈነ አምላክ ወልደ አምላክ የተስፋውን ቃል ለመፈጸም ከውድቀታችን ሊያነሳን ያን የተራቆተ ሥጋችንን ለበሰልን። የሚካኤል ሠራዊት በፍርኃት የገብርኤል ሠራዊት በመንቀጥቀጥ የሚያመሰግኑት እርሱ ዕርቃኑን በመካከላችን ተገኘ።

🍁 ወበቤተልሔም ወጽአ እምከርሰ እሙ ዕራቁ (በቤተልሔም ከእናቱ ማሕፀን ዕርቃኑን ተወለደ)

መጽሐፍ "ዕራቅየ ወፃእኩ እምከርሠ እምየ" እንዳለ እኛን በሚመስልበት የተዋህዶ ግብር ከድንግል እናቱ ማሕፀን ዕርቃኑን ተወለደ፤ ከመለኮቱ ሳይራቆት (ዕሩቅ ብእሲ ሳይሰኝ) ከሥጋ ልብስ ባዶ ሆኖ ተራቁቶ ፣ ክብሩን በፈቃዱ ትቶ በትህትና ወደምድራችን መጣ። ይህን ሥጋችንን ለብሶ የሰው ልጅ መባሉ ያንን የሰማይ ክብር እርሱን በጸጋ ለብሰን ትርሲተ ወልድ / የሥጦታ ልጆቹ ሊያሰኘን ነውና።

የመጽሐፉም ምስክርነት እንዲህ የሚል ነው "አሰረቶ መንኮብያቲሁ ወአስከበቶ ውስተ ጎል ወጠብለለቶ በጽርቅት ⇨ አውራ ጣቱን አሰረችው ፣ በግርግም አስተኛችው፣ በመጠቅለያም ጠቀለለችው” [ሉቃ ፪፥፯]

የ፲፭ ዓመቷ ገሊላዊት ብላቴና እናቱ ድንግል ማርያም በከብቶቹ ማደርያ ስትወልደው ለብኩርናው አውራ ጣቱን አሥራ፣ የተራቆተ ሰውነቱን በጨርቅ ጠቅላላ ፣ ለመኝታው ግርግም አሰናድታ ባላትና ባገኘችው ተቀበለችው። ይህም ለእኛ የተከፈለው ካሣ እረኞችም ምልክት እንዲሆናቸው በመልአኩ በኩል ‘እሱረ መንኮብያት ፣ ስኩብ ውስተ ጎል ፣ ጥብሉል በአጽርቅት (አውራ ጣቱ የታሠረ ፣ ከግርግም የተኛ ፣ በጨርቅ የተጠቀለለ) ሕፃን በበረቱ ታገኛላችሁ’ ተባሉ። [ሉቃ ፪፥፲፪]

ልጇን ጌታዬ የምትል ብቸኛዋ የፈጣሪ እናቱ የአምላክ ወላዲቱ ለዕርቃኑ መክደኛ የበለስ ቅጠል ስላገኘችበት ተኣምራታዊ መንገድ በቤተክርስቲያናችን ቅዱስ ትውፊት
እንዲህ የሚል አብነት አለ
«በለሶን ዕፀ አእምሮ የሚባለው ነው፤ ይህ የገነት በለስ አዳምና ሔዋን ፍሬውን በልተው ቅጠሉን የለበሱት ኋላም የልደት ዕለት በተኣምራት መልአክ (ቅዱስ ገብርኤል) አምጥቶላት ዳግሚት ሔዋን ድንግል ማርያም ለልጇ ለዳግማይ አዳም ሥግው ቃል ክርስቶስ ያለበሰችው ነው፤ ቅዱስ ያሬድ በድጓው "ከደነቶ እሙ ቄጽለ በሰሶን" እንዳለው። ስለዚህ ምሥጢር ብዙዎች ብዙ ብለዋል!

ባለቅኔው ፦
በለሰ ገነት ለአዳም ወሔዋን መቲሮቶሙ
መንክረ ልደት አምላከ መንገሌሆሙ ሰሐበ
ወገብርኤልሃ ዜናዊ ቀጸበ
እንተ ከመዝሰ ግብር እምከመ ለአዳም ተውህበ
ወረከበት ሔዋን ዘኢተረክበ
ካዕበ ይስሐብ ኀቤሆሙ አበ
ለበለሰ ይምትርዎ ካዕበ

ደራሲው ፦
ሰላም ለኵልያቲክሙ ዕሩያነ አካል ወአምሳል፥
አቅርንተ ነቢያት ሥላሴ ዘድምጽክሙ ወንጌል፥
ኢሳይያስ ጸርሐ ወይቤ ውስተ መካነ ላሕም ጎል፥
ገብርኤል አወፈየኒ ሕፃነ ማርያም ድንግል፥
በቆጽለ በለሶን ክዱን ወበጸርቅ ጥብሉል

🍁 ወበዮርዳኖስ ተጠምቀ በማይ ዕራቁ (በዮርዳኖስ ዕርቃኑን በውኃ ተጠመቀ)

ለኃጢዓታችን ሥርየት የሚሆን በግዕ ዘመስዋዕት፣ ለነፍሳችን ጠባቂዋ እረኛ ሊቀ ኖሎት፤ ወልዱ ለቡሩክ: ከሣቴ ብርሃን የዓለም መድኃኒት በባርያው በዮሐንስ እጅ እንዲጠመቅ ወደ ዮርዳኖስ ሲገባ ከልብሱ መራቆቱን የአበው መጽሐፍ እንዲህ ይገልጣል

"አስተርአየ በውስተ ዮርዳኖስ እንዘ ክሡት ዕርቃኑ ለተጠምቆ ⇨ ለመጠመቅ ራቁቱን በዮርዳኖስ ባሕር ውስጥ ታየ" (መጽሐፈ ምሥጢር)

የዮርዳኖስ ጥምቀት የሁላችን ዕርቃን የተከደነበት ነው።

🍁 ወበቀራንዮ ሰቀልዎ ዲበ ዕፅ ዕራቆ (በቀራንዮ በእንጨት ላይ ዕርቃኑን ሰቀሉት)

አባ ጊዮርጊስ ስለዚህም እንዲህ ብሏል “ወበከመ ተከሥተ ዕርቃነ አዳም ማእከለ ዕፀዊሃ ለገነት ከማሁ ተከሥተ ዕርቃነ ትስብእቱ ለመድኃኒነ ማዕከለ ጉባኤሆሙ ለማኅበረ እስራኤል ⇨ አዳም በገነት ዛፎች መካከል ርቃኑን እንደታየ እንደሁም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ በሰውነቱ በአይሁድ ጉባኤ መካከል ዕርቃኑን ሆኖ ታየ” (መጽሐፈ ምሥጢር)
በደራስያኑም የመልክእ ምስጋና እንዲህ ተገልጧል፦

ሰላም ለዕርቃንክ እምልብሰ እልታሕ ወሰንዱን
እስከነ ሰሐቁ ላዕሌከ ሐራ ጲላጦስ መስፍን
ክርስቶስ ክቡር በቅድመ አይሁድ ምኑን
ክድነኒ እግዚኦ ልብሰ ተፋቅሮ ብርሃን
እስመ ፍቅር ተዓቢ እምኵሉ ሥልጣን
[መልክኣ ማኅየዊ ዘውእቱ መልክአ ኢየሱስ ካልእ]

ሰላም ለዕርቃንከ ዘአዕረቅዎ አይሁድ፤
እምልብሰ ምድራዊ ግዙፋነ ክሣድ፤
ዕሥራኤል እሙንቱ ሕዝብ ክቡድ፤
ተማኅፀነ በዕርቃንከ ከመ ትዕቀበነ ወልድ፤
አንተ አቡነ ወንሕነ ውሉድ። [መልክኣ ቅንዋት]

ቅዱስ ያሬድም በፋሲካው ድጓ እንዲህ ይላል
“ሰአሎ ዮሴፍ ለጲላጦስ ወይቤሎ
#ሀበኒ_በድኖ_ለኢየሱስ
#ከመ_እክድን_ዕቃርኖ_በልብስ
#ለዘከደነ_ዕርቃንየ_በዮርዳኖስ - ዮሴፍ ለጲላጦስ እንዲህ አለው፡- በዮርዳኖስ እርቃኔን የሸፈነውን እርቃኑን በልብስ እሸፍን ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ ስጠኝ”

ዮሴፍና ኒቆዲሞስ እንደ ሰብአ ሰገል ምንኛ እድለኞች ናቸው? የአምላኩን እርቃን የሚሸፍን የራሱን ዕርቃን የሚከድን ነው።

እነርሱስ ከመስቀል ለማውረድ በአዲስ መቃብር ለማኖር ዕርቃኑን ለመክደን ሰውነቱን ለመሸፈን ጠይቀው ተፈቀደላቸው!

ታዲያ እኛስ …

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13088

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

What is Telegram Possible Future Strategies?

Cryptoassets enthusiasts use this application for their trade activities, and they may make donations for this cause.If somehow Telegram do run out of money to sustain themselves they will probably introduce some features that will not hinder the rudimentary principle of Telegram but provide users with enhanced and enriched experience. This could be similar to features where characters can be customized in a game which directly do not affect the in-game strategies but add to the experience.

How to Invest in Bitcoin?

Like a stock, you can buy and hold Bitcoin as an investment. You can even now do so in special retirement accounts called Bitcoin IRAs. No matter where you choose to hold your Bitcoin, people’s philosophies on how to invest it vary: Some buy and hold long term, some buy and aim to sell after a price rally, and others bet on its price decreasing. Bitcoin’s price over time has experienced big price swings, going as low as $5,165 and as high as $28,990 in 2020 alone. “I think in some places, people might be using Bitcoin to pay for things, but the truth is that it’s an asset that looks like it’s going to be increasing in value relatively quickly for some time,” Marquez says. “So why would you sell something that’s going to be worth so much more next year than it is today? The majority of people that hold it are long-term investors.”

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from ar


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA